Thursday, April 2, 2026

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ስምንት ዓመታት በሥልጣን ማማ ላይ


Wednesday, April 1, 2026

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ስምንት ዓመታት በሥልጣን ማማ ላይ

(በበፍቃዱ ዘ. ኃይሉ)

ዐቢይ አሕመድ ተቃዋሚ መስለው፣ ተቃዋሚ ለብሰው ሥልጣን ከተቆናጠጡ እነኾ ዛሬ ድፍን ስምንት ዓመታቸው።

ዐቢይ አሕመድ ጠቅላይ ሚኒስትር ከሆኑ ወዲህ በየሁለት ዓመቱ አስተዳደራቸውን የሚገመግም መጣጥፍ እየጻፍኩ ነው። ዘንድሮም ባሕሉን ለማስቀጠል ይህንን መጣጥፍ እነኾ ብያለሁ። በቅድሚያ የቀደምት ጽሑፎቼን ዐውድና ምላሽ በጨረፍታ ላስታውሳችሁ።


ዐቢይ አሕመድ በሥልጣን ጎዳና ሁለት ዓመት ሲሞላቸው በጻፍኩት ጽሑፍ  ሃይማኖታዊ ሰበካን ከአነቃቂ ንግግር ጋር በሚቀይጥ የንግግር ዘይቤያቸው አታላይ አንደበት አባታዊ (paternalistic) አገዛዝ ስርዓት እንደገነቡ ለመከራከር ሞክሬ ነበር፤ ክርክሬ መንግሥታቸው እኛን ዜጎቹን ልክ በራሳቸው መወሰን የማይችሉ ሕፃናት ይመለከተናል የሚል ነበር። ይህንን ጽሑፍ በጻፍኩበት ወቅት ዐቢይ አሕመድ በመሐል አገር ከፍተኛ ድጋፍ ስለነበራቸው፣ ምንም እንኳን ትችቴ የመረረ ሊባል የሚችል ዓይነት ባይሆንም እንዲህ ያለ ትችት ከመሐል አገር ሰው ጭራሹኑ አልተለመደም ነበርና ከአንዳንድ ወዳጆቼም ሳይቀር ብዙ ነቀፌታዎችን አስከትሎብኝ ነበር። 


አራት ዓመት ሲሞላቸው የጻፍኩት ግን በተቃራኒው የመረረ ትችት ሊባል የሚችል ነበር። “ከድጡ ወደ ማጡ” የሚል ርዕስ የሰጠኹት ሲሆን፣ መጀመሪያ በፍትሕ መጽሔት ላይ የሽፋን ገጽ ታሪክ (cover-story) ሆኖ ታትሟል። ከዚያም በብዙ ዩቱብ ገጾች ተባዝቷል። በወቅቱ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ፈተና ውስጥ የገባችበት ነበር። የእርሳቸውን አራት ዓመታት ስገመግመው፣ ዐቢይ አሕመድ የብልፅግና ፓርቲ ብቸኛ ሰው መኾንን “ፓርቲው ራሳችው ናቸው” በሚል በመግለጽ - ወደ ፈላጭ ቆራጭነት ማደጋቸውን፣ ትግራይ ከኢትዮጵያ ወደ መሰናበት እያመራች መሆኗን፣ ኦሮሚያ አኬልዳማ ሊያስብላት የሚያስችል በታጣቂዎችና መንግሥት መሐል የተያዘ ሕዝብ መኖሩን፣ እና የሕግ የበላይነት መንኳሰስ እና የነውጠኝነትን መንሰራፋት (እንዲሁም  የእርሳቸውን አመራር “የነውጥ ቀዛፊነት” በሚል) ጠቅሼ - ለዚህ ሁሉ ዋናው ተጠያቂው እርሳቸው መሆናቸውን ደምድሜ ጻፍኩ። ይህን ጊዜ ብዙ ወዳጆቼ “ክክፉ ይጠብቅህ” ከማለት በቀር ከድምዳሜዬ እምብዛም የተለየ ድምዳሜ አልነበራቸውም። 


ስድስት ዓመት ሲሞላቸው “እየሰጡ መንሳት” የዐቢይ አሕመድ የአመራር ዘይቤ ነው የሚል ትንታኔ ጻፍኩ። በስድስት ዓመታት አስተውሎቴ፣ ዐቢይ አሕመድ በፖለቲካ አመለካከታቸው እና እንቅስቃሴያቸው የታሰሩ ሰዎችን ሲፈቱ አይተናል፤ መልሰው ደግሞ የርሳቸውን ፖለቲካ የሚቃወሙ ሰዎችን በየሰበብ አስባቡ በመንግሥታቸው ሲያሳስሩ አይተናል። ብዙኃንን ያስፈነደቁ የሰላም ስምምነቶች ውስጥ ሲገቡ አይተናል (ኤርትራ፣ ትግራይ)፤ እነዚያ የሰላም ሥምምነቶች መልሰው ውኃ ሲበላቸው አይተናል። እነዚህ እና መሰል የአመራር ዘዬአቸው መገለጫ  - እየሰጡ መንሳት - ሊባል እንደሚገባ ትንታኔዬን አቅርቤያለሁ። ይሄም ጽሑፍ በመጠኑ አንባቢ አግኝቷል። ተባዝቷልም።  


ዐቢይ አሕመድ አሁንም ገና እየተገለጡ ነው።  ትንታኔያችንም ይቀጥላል።


Lost in Transition” ባሰኘሁት መጽሓፌ ውስጥም የዐቢይ አሕመድ አነሳስ (The Rise of Abiy Ahmed) በሚል ርዕስ የ18 ገጽ ትንታኔ አስቀምጫለሁ። በዚህ ትንታኔዬ ዐቢይ በምን ዓይነት ውስጣዊ እና ውጪያዊ ትግሎች ወደ ከፍተኛው የሥልጣን ማማ እንደተወጣጡ ለመተንተን ሞክሬያለሁ። ዐቢይ አሕመድ በብዕር ሥም ያሳተሙትን “እርካብና መንበር” አንብቤያለሁ። በሥማቸው ያሳተሟቸውን “የመደመር” ተከታታይ መጽሓፎችንም አንብቤያለሁ። ቶም ጋርድነር “The Abiy Project” በሚል ርዕስ የጻፈውን ባለ ትልቅ ጥራዝ መጽሓፍም አንብቤያለሁ። የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን እየሰበሰቡ የሚያደርጓቸውን ንግግሮችም እያሳደድኩ፣ ጊዜ በፈቀደልኝ ቁጥር ላደምጣቸው ሞክሬያለሁ። በነዚህ ሁሉ ንባቦቼ የተረዳሁት ዐቢይ አሕመድ የፈለጉትን ከማድረግ ምንም የማያስቆማቸው ሰው መሆናቸውን ነው ማለት እችላለሁ። ከዚህ በታች የምጽፈው እና ከዚህ ውጪም የምሰጣቸው አስተያየቶች በነዚህ ጥረቶቼ የወሰድኳቸው ግምገማዎቼ መሆናቸውን ቀድሜ ለማሳወቅ እወዳለሁ። 


ከ“ቲም ለማ” ወደ “መጋቢታውያን”


ለውጡን ስታስቡ ከ"ቲም ለማ" ውጪ ማሰብ ትችላላችሁ? ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ግን ይችላሉ። “የመደመር መንገድ” የሚለው መጽሐፋቸው ስለለውጡ አመጣጥ የሚተነትን ነው። ዐቢይ ለውጡን ለማምጣት የዐሥር ዓመት ሴራ እንደተሠራ ይናገራሉ። አምናቸዋለሁ። ከባድ ሚዛን “የሸዋ ፖለቲካ” ተጫዋች ናቸው። በአንድ እግራቸው ከገዢው ፓርቲ መንደር፣ በሌላ እግራቸው ከተቃዋሚዎች መንደር ቆመው ነው ጨዋታውን የተጫወቱት፤ ለዚህ ነው መግቢያዬ ላይ “ተቃዋሚ መስለው፣ ተቃዋሚ ለብሰው” የሚል ገለጻ የተጠቀምኩት። እንደ እርሳቸው አባባል እኛ “አሮማራ” የምንለው ሕወሓትን ለመገርሰስ የተፀነሰው ትብብር በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የተመራው ልዑክ ራሺያ ሲጓዝ በዐቢይ እና ደመቀ የተጠነሰሰ ሴራ ነው። ስለዚህ ለለውጡ፣ የለማ መገርሳ ሚና እምብዛም እንዳልነበር እንደዋዛ ታልፏል። የመደመር መንገድ መጽሐፍ የለማን ስም አንድ ሁለቴ እንደዋዛ (anecdote) አንስቶ ነው የሚያልፈው። ይልቁንም መጽሓፉ ላይ ደመቀ መኮንን የተሻለ ተጠቅሰዋል። ዐቢይ፣ በዚህ መጽሐፍ ላይ “ቲም ለማ” የሚለውን የለውጥ ቡድን መጠሪያ ስም፥ “መጋቢታውያን” በሚል ሊተኩት ሞክረዋል። መጋቢት፣ እርሳቸው የተመረጡበት ወር ነው። በርግጥ ደመቀ መኮንን ከእጩነት ራሳቸውን ባልተጠበቀ መንገድ ባያገልሉ ኖሮ፣ ዐቢይ አሕመድ በሰፋ የድምፅ ብልጫ የማሸነፍ ዕድላቸው አጠያያቂ ይሆን ነበር፤ ስለዚህ የደመቀ መኮንንም መጠቀስ ትርጉም ይሰጣል። የለማ መገርሳ ግን እንደዋዛ ከታሪኩ መፋቅ በጣም አስገርሞኛል። ዐቢይ "ቲም ለማ" ከሚለው ይልቅ "መጋቢታውያን" የሚለውን መጠሪያ የወደዱት በለማ ስም መጠራቱ የእርሳችውን ሚና የሚያሳንስ ስለመሰላቸው ወይስ ከለማ መገርሳ ጋር መንገዳቸው ስለተለያየ?

ከ[ቀዳማዊ] ኢሕአዴግ ወደ ብልፅግና (ራብአዊ ኢሕአዴግ)


ኢሕአዴግ ከምርጫ 97 በፊት እና በኋላ አንድ አይደለም። ከምርጫ 97 በፊት ትርፍና ኪሳራው ሲወራረድ በዴሞክራሲያዊነት ረገድ ቀዳማዊ ኢሕአዴግ አዎንታዊ ደረጃዎችን አስመዝግቧል። ነፃ ሚዲያዎች እና ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በሰፊው የሚንቀሳቀሱበት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተደራጅተው የሚወጡበት ምኅዳር ፈጥሮ ነበር። ከምርጫ 97 በኋላ ያንን ምኅዳር መልሶ መቀልበስ ጀመረ፤ አሳሪ ሕጎች ወጡ፣ ዜጎች በፍርሐት ካቴና ታሰሩ። የተቃውሞ ፖለቲካ (opposition politics) ወደ እምቢተኝነት ፖለቲካ (resistance politics) ተቀየረ እና የ2010ሩ ለውጥ መጣ። ለውጡ የመጣው በተቃውሞ ግፊያ ቢሆንም፣ በኢሕአዴግ ውስጥ ከተደረገው ውስጣዊ ትግል ውጪ እውን ሊሆን አይችልም ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የተመረጡት በኢትዮጵያ ሕዝብ አልነበረም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍትሓዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለማድረግ አልታደለም። ይልቁንም፣ በኢሕአዴግ ውስጥ በነበረ የፓርቲ ውስጥ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ነው። ኢሕአዴግ እስከ 2011 አጋማሽ ድረስ ግንባር ሆኖ ዘልቋል። 


ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ “ጠርዝ ላይ” በሚል ባሳተሙት መጽሓፍ ሁለቱን ኢሕአዴጎች ሲያወዳድራቸው “ቀዳማዊ ኢሕአዴግ” እና “ዳግማዊ ኢሕአዴግ” በሚል ጠርተዋቸው ነበር። ነገር ግን የኢሕአዴግ አገዛዝም ቢሆን ቅድመ እና ድኅረ ምርጫ 97 መካከል ልዩነት ስለነበረው፣ የቅድመ ምርጫ 97ቱን “ቀዳማዊ” እንበለው፣ የድኅረ ምርጫ 97ቱን ደግሞ እስከ 2010 “ዳግማዊ” እንበለው እና ከ2010 እስከ ብልፅግና ያለውን “ሳልሳዊ” እንበለው። ቀዳማዊ ኢሕአዴግ ውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲ ያልነበረው፣ ነገር ግን ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ባሕሎችን ያለማመደ ግንባር ነበር። ዳግማዊ ኢሕአዴግ ውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊነቱ እየጎለበተ የመጣ (ምሳሌ የሕወሓት የበላይነት እየተሞገተ የነበረበት እና የሥልጣን ክፍፍል በግንባሩ አባላት መካከል እየተስተካከለ የነበረበት እና ለአዲሱ የኢሕአዴግ ትውልድም ሥልጣን ማጋራት የጀመረበት ጊዜ ነበር)፣ ነገር ግን አገራዊ አፋኝነት የተፋፋመበት (ለምሳሌ ቢሮክራሲው እና ፓርቲው የተጋቡበት) ነበር። ሳልሳዊ ኢሕአዴግ ደግሞ ከድኅረ 97 በኋላ የነበሩ ጥፋቶች እርምት የሚመስል እርምጃ የተወሰደበት ነበር። እስረኞች ተፈቱ፣ አፋኞቹ ሕጎች መከለስ ጀመሩ፣ ያኮረፉ የፖለቲካ አካሎች ለእርቅ ተጋበዙ፣ የተሰደዱ ተመለሱ፣ የተጣሉ ታረቁ፣ ፓርቲውና ቢሮክራሲው ተፋትተው ባለሙያዎች (ሜሪቶክራቶች) በገፍ ተቀጠሩ (የፓርቲ አባላት ያልሆኑ ባለሙያዎች ሚኒስትር ዲኤታ ሆነው በገፍ የተቀጠሩበት ጊዜም ነበር)። ይህ ግን የቀጠለው ለአጭር ጊዜ ብቻ ነው፤ ከዚያ ራብአዊ ኢሕአዴግ ተወለደ። ሳልሳዊ ኢሕአዴግ ብዙ አሳይቶናል፤ ተስፋም ሰጥቶን ነበር። ግን ዕድሜው አጭር ነው።


ራብአዊ ኢሕአዴግ (ብልፅግና ፓርቲ) ኢሕአዴግ እና አጋሮቹ ሲቀነስ ሕወሓት ማለት ነው። ዛሬ ብልፅግና ውስጥ የምናያቸው ቁልፍ ሰዎች፣ ከጥቂት በሳልሳዊ ኢሕአዴግ ጊዜ ከተቀላቀሉት እንግዶች በቀር ነባር ኢሕአዴጋውያን ናቸው። ስለዚህ ብልፅግና ሙሉ ለሙሉ ከኢሕአዴግ የተነጠለ አድርጎ ማሰብ ስህተት ይሆናል። ይልቁንም፣ ሌሎቹ የግንባሩ አባሎች የሕወሓት ታናሽ (junior) አጋር ተደርገው ይታዩ ነበር። ዛሬ የብልፅግና መሠረት ሆነው የምናያቸው እነዚህን ነው። ዐቢይ አሕመድም የኢሕአዴግ ሚኒስትር እስከመሆን የደረሱ ጉምቱ ናቸው። ነገር ግን ይህንን ታሪካቸውን ማረሳሳት ችለዋል። ዕድሜ የሕዝብን ቀልብ ለገዛው ሳልሳዊ ኢሕአዴግ!


ራብአዊ ኢሕአዴግ የቀዳማዊ ኢሕአዴግን ውስጠ ፓርቲ አፋኝነት እና የዳግማዊ ኢሕአዴግን አገራዊ አፋኝነት አጣምሮ ይዟል። በራብአዊ ኢሕአዴግ ውስጠ ትግል አድርጎ መሪ መለወጥ ቢያንስ በቅርቡ አይቻልም። በቀዳማዊ ኢሕአዴግ አብዮታዊ ዲሞክራትነት፣ በዳግማዊ ኢሕአዴግ ልማታዊ መንግሥትነት መንግሥታዊ ዲስኩር ነበር፤ እነዚህኞቹን ኢሕአዴጎች ምን፣ እንዴት፣ ለምን እንደሚወስኑ መገመት (predictability) ትችላላችሁ። በሳልሳዊ ኢሕአዴግ ሊበራሊዝም መሰል ነገር፣ በራብአዊ ኢሕአዴግ ደግሞ “ሰንበሌጣዊነት” ይስተዋላል፤ ብልፅግና ርዕዮተ ዓለም የለውም። ይህንን ፓርቲው በይፋ አውጆታል። ይህንን አንድ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር “ሰንበሌጣዊነት” ይለዋል፤ በነፈሰበት መንፈስ። አንዳንዴ “መደመር” የሚባል ዲስኩር ርዕዮተ ዓለምን ሊተካ ይሞክራል። ነገር ግን አንድም ምሁር በመደመር “ፍልስፍና” የብልፅግናን ፖለቲካ ለመተንተን አይሞክርን። ምክንያቱም ሐሳቡ ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት ከመንፈሳዊ አነቃቂ ንግግርነት አያልፍም።


ግን ደግሞ በነፈሰበት መንፈስ ስንል ራብአዊ ኢሕአዴግ ድርቅ የሚልባቸው አቋሞች የሉም ማለት አይደለም። በሥልጣኑ እና በከተማ ውበት ጉዳይ ከማንም ጋር አይደራደርም - ፓርቲው፣ AKA መሪው፣ ዐቢይ አሕመድ። የሆነ ሆኖ ኢሕአዴግ በሰላማዊ መንገድ መሪ ቀይሯል። ብልፅግና በውስጣዊ ትግል መሪ መቀየር የሚችል ይመስላችኋል? እኔ ግን ይኼ የሚሆንበት ዕድል በቅርብ ርቀት አይታየኝም።


ከለውጥ ወደ ነውጥ 


የ2010ሩ ክስተት መጀመሪያ የመንግሥት ለውጥ ነበር። ነገር ግን ዘመኑ የመንግሥት ባለሥልጣናት እንደሚሉት 'የለውጥ' ከሚባል ይልቅ የ'ነውጥ’ ቢባል የተሻለ የሚያስኬድ ይመስለኛል።


ነውጡ የጀመረው ግለሰቦችን በድንጋይ በመውገር እና በአደባባይ ላይ ዘቅዝቆ በመስቀል በታጀበ የመንጋ ጥቃት (mob violence) ሲሆን፤ በመቀጠልም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ያፈናቀለ ብሔርን መሠረት ያደረገ ግጭት፣ ከዚያም የአማራ ክልል ፕሬዚዳንትን እና የካቢኔ አባሎቻቸውን፣ እንዲሁም አባ ቶርቤ በተባለ ገድሎ አደር የኅቡዕ ድርጅት የሚገደሉ ባለሥልጣናት፣ ከዚያም ታዋቂውን የኦሮሚያ ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳን በመሳሰሉ ግለሰቦች ላይ ባነጣጠረ የፖለቲካ ግድያ ተስፋፍቶ፣ በስተመጨረሻም በትግራይ ወደተካሄደው ሙሉ ጦርነት አምርቷል። የትግራዩ ጦርነት በሰላም ሥምምነት የተጠናቀቀ ቢመስልም፣ ይህንኑ ተከትሎ በአማራ ክልል በታጠቁ ቡድኖች እና በመንግሥት መካከል ውጊያ ፈንድቷል። በኦሮሚያም በታጠቁ ቡድኖች እና በመንግሥት መካከል የሚደረገው ውጊያ ከትግራዩ ጦርነት በፊት ጀምሮ እስካሁንም ቀጥሏል። በመሆኑም የሽግግሩን ጊዜ የሚገልጸው "ነውጥ" የሚለው ቃል ነው ማለት ተገቢነት አለው።


ለዚህ “ዘመነ ዕብደት” ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለብቻቸው ተጠያቂ ማድረግ አግባብ አይደለም፤ ሁላችንም የየራሳችን ድርሻ አለን። ነገር ግን ዋነኛ ተጠያቂ እርሳቸው ናቸው ቢባል ማጋነን አይሆንም። የደቦ ፍርዶች እና የደቦ ፍርዶችን የሚቀሰቅሱ ንግግሮቻቸው መሳ ለመሳ መሔዳቸውን አስተውያለሁ። በመጽሐፌ እንዳመለከትኩት፣ እርሳቸው በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ወጥተው ወጣቶች አካባቢያቸውን "ከፀጉረ ልውጦች" እንዲጠብቁ ባሳሰቡ ጥቂት ቀናት ውስጥ የጀመሩ የደቦ ፍርዶች ወደ ወል ግጭቶች አድገው ለወራት ዘልቀዋል። በወቅቱ የመንግሥታቸው ትርክት በአንድ በኩል ለሁሉ ነገር ሕወሓት ላይ ጣት የሚቀስር፣ ካልሆነ ደግሞ ታስሮ የቆየ ብዙኃን ነፃነት እና ዴሞክራሲን መሸከም እንዳቃተው የሚያመላክት ነበር፤ ይህም የሕግ የበላይነት ማስከበር የነበረበት መንግሥት ኃላፊነቱን ባለመወጣቱ የተከሰተውን ቀውስ ለማስቀየሻነት የዋለ ይመስለኛል። የሆነ ሆኖ፣ ነውጡ እና ሁካታው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ኃይል ማከማቻነት ውሏል። ያሻቸውን እርምጃ ቢወስዱ፣ ማንም ምንም የማይታዘባቸው ወቅት ነበር።


ይህ በእንዲህ እንዳለ ነውጦቹ ስፋታቸው እያደጉ መጡ። የሚያስገርመው ግን፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ነውጡን ጀመረውም አልጀመረውም፣ የዐቢይ አሕመድ አስተዳደር ግን ሥልጣኑን ለማጠናከር ሁሉንም አጋጣሚዎች ተጠቅሞባቸዋል። መንግሥታቸው የ[መንጋ] ጥቃት መስፋፋትን የሕግ የበላይነትን ወደ ጎን ለማለት እንደ ማመካኛ ተጠቅሞበታል። በስምንት ዓመታት የሥልጣን ዘመናቸውም ሦስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጆችን አውጀዋል። መንግሥት ውይይት እና ድርድርን ከማድረግ ይልቅ ነውጥን እንዲመርጥ በማበረታታት፣ ነውጥን ሥልጣኑን ለማጠናከር እንዴት እንደተጠቀመበት ተጨማሪ ጥቂት ምሳሌዎች እንመልከት።


አንደኛ፣ መንግሥት በኦሮሚያ የተከሰተውን ነውጥ ዋነኛውን የኦሮሚያ የፖለቲካ ፓርቲ የሆነውን የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) እንዲከፋፈል ለማድረግ እና የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስን (ኦፌኮ) ለማዳከም ለሚያደርገው እንቅስቃሴ እንደ ማመካኛ ተጠቅሞበታል። በርካታ የኦነግ አመራሮች ፍርድ ቤት በነፃ ካሰናበታቸው በኋላ ለበርካታ ወራት በእስር ላይ ቆይተዋል። ይህንን የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድም፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶችም ያረጋገጡት ነገር ነው። በምርጫ 2013 ኦነግ እና ኦፌኮ ከምርጫ “ተገፍተናል” ብለው ሲወጡ የሰጡት ምክንያት እነዚህን ክስተቶች ሽፋን በማድረግ የብልፅግና መንግሥት አባላት እና አመራሮቻችንን አስሯል፣ የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶቻችንን ዘግቷል፣ መጫወቻ ሜዳችንን አጥብቧል በሚል ነበር።


በ2012 የሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ የተቀሰቀሰውን ነውጥ ምክንያት በማድረግ እንደ ጃዋር መሐመድ (ከኦፌኮ) እና እስክንድር ነጋ (የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ በአዲስ አበባ) ያሉ ታዋቂ የተቃውሞ መሪዎችን መንግሥታቸው አስሯል። እነዚህ ሁለቱ ግለሰቦች በቅደም ተከተል በኦሮሚያ እና በአዲስ አበባ በተካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት ትልቅ ተቃውሞን ሊመሩ ይችሉ ነበር። እነሱ በእስር ላይ እያሉ ገዥው ፓርቲ ምርጫውን በአብላጫ ድምፅ አሸንፏል (በወቅቱ በኦሮሚያ ሁሉም ተቃዋሚዎች ተደምረው ያቀረቡት የእጩ ብዛት ከጠቅላላው የእጩዎች ብዛት 35% ብቻ ነበር፤ በኦሮሚያ ብልፅግና ብቻውን ነበር የተወዳደረው ቢባል ማጋነን አይደለም)። ከዚያም ከአንድ ዓመት ተኩል ገደማ እስር በኋላ፣ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ክሳቸውን በማቋረጡ ጃዋር እና እስክንድር እንዲሁም አብረዋቸው የተከሰሱ ግለሰቦች ከእስር ያለ ፍርድ ተፈትተዋል። ይህም መንግሥት አስቀድሞ ግቡን ስላሳካ ተጠርጣሪዎቹን እስር ቤት ማቆየት የማይፈልግበት ሰዓት ሲደርስ እንደለቀቃቸው ያስጠረጥራል። በዚህ መሐል የተዘነጋው 200 ያህል ሕይወት የቀጠፈውን ነውጥ ተጠያቂ አካል አለመኖሩ ነው። 


አሁን ላይ እስክንድር ነጋ በአማራ ክልል የትጥቅ ትግል መሪዎች አንዱ ሲሆን፣ ጃዋር ደግሞ በዳግም ስደት ወደ በይነመረብ አክቲቪዝም ተመልሷል። በመሆኑም ሁለቱም በለውጡ ሰሞን ከቀሰቀሱት ሕዝባዊ መሠረታቸው በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ እንዲርቁ ተደርገዋል።


ሌላኛው ምሳሌ የትግራይ ጦርነት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የትግራዩን ጦርነት ተከትሎ ሕወሓትን እና አጋሮቹን ከመንግሥት ቢሮክራሲ እና ከደኅንነት መዋቅሩ አስወግደዋል፤ ይህ ማለት መንግሥታቸው ክፍት የሆኑትን ቦታዎች በታማኞቹ በመተካት በመንግሥት ሥርዓቱ ውስጥ ሊገጥመው የሚችለውን ተግዳሮት ቀንሷል ማለት ነው። በተጨማሪም መንግሥታቸው የመንግሥት እና የገዢው ፓርቲ ሚዲያዎችን እንዲሁም ማኅበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ዒላማ ባደረጋቸው አካላት ላይ ሰፊ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ያካሒዳል። እንዲሁም የደኅንነት መዋቅሩን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሯል። አሁን፣ የትግራይ ጦርነት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሕይወቶችን ከቀጠፈ በኋላ በሰላም ስምምነት (ለጊዜው) ተጠናቋል፤ እርግጥ ነው ይህንን ጽሑፍ ስጽፍ ሌላ ጦርነት ሊጀመር ይችላል የሚል ስጋት በሰፊው እያንዣበበ ነው። የሆነ ሆኖ፣ ከጦርነቱ በፊት ሕወሓት የነበረው አቅም አሁን ሞቷል። ሕወሓት ለዐቢይ አሕመድ ሥልጣን ይኼ ነው የሚባል ስጋት አይፈጥርም።


ነገር ግን የዐቢይ መንግሥት አሁንም ሕወሓቶችን ለመውጋት አጋር እንዲሆኑት የታገሳቸው ኃይሎች ይቀሩ ነበር። ዐቢይ አሕመድ ከመምጣታቸው በፊት የነበሩት ክልላዊ ልዩ ኃይሎች የሶማሊ ልዩ ኃይሎች ብቻ ነበሩ። ከዐቢይ አሕመድ መምጣት በኋላ ግን ልዩ ኃይሎች በየክልሉ ፈሉ። ልዩ ኃይሎቹ በርግጥም ለአገራዊ ሰላምም፣ ለመንግሥት ሥልጣንም አደጋ ነበሩ (የአማራ ክልል መሪዎችን መገደል፣ በሶማሊና ኦሮሚያ ክልሎች ድንበሮች የነበሩ ግጭቶች፣ አፋር እና ሶማሊ፣ ወዘተ ዋቢ አርጎ መጥቀስ ይቻላል)። ነገር ግን ለትግራይ ጦርነት አጋር እንዲሆኑ ሲባል ቸል ተብለው ነበር። በተጨማሪም እንደ “ፋኖ” ያሉ ታጣቂ ቡድኖችም በይፋ ወደ ጦርነቱ ተጋብዘው ነበር። ችግሩ የመጣው ጦርነቱ ሲጠናቀቅ ነው። ታዲያ የዐቢይ አሕመድ መንግሥት ትኩረቱን ወደ እነዚህ በመቀየር፣ በድንገት መበተናቸውን አሳወቀ። ይህም በተለይ በአማራ ክልል ዛሬ ለተገባበት አሰቃቂ ውጊያ ምክንያት ሆነ። የትግራዩም ይሁን የአማራ ክልሎቹ ውጊያዎች፣ ቢያንስ እስካሁን፣ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ሥልጣን ይልቅ የክልሎቹን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቁመና ነው ያናጉት። እያንዳንዱ ነውጥ እና ነውጥ አዘል ግጭት በእርሳቸው ሥልጣን ዙሪያ ያደረሰው ጉዳይ ምናልባት የገጽታ እንጂ የኃይል ሚዛን መዛባት አይደለም።


እነዚህን ኹነቶች ስንገመግም  'ለውጡ' ከሚለው ቃል እኩል ውይም በላይ 'ነውጡ' የሚለው ቃል ዘመናቸውን ይገልጸዋል። ለውጡ ነውጡ ነው።


ለትንታኔ አስቸጋሪው ዐቢይ


ዐቢይ አሕመድ ወደ ሥልጣን የመጡበት ዘመን በማኅበራዊ ሚዲያ አተራማሽነት (disruption) ሲጦዝ፣ እንዲሁም የምዕራባውያንን ኃያልነት በምሥራቃውያን ኃያልነት (ቻይና) ተግዳሮት ሲገጥመው ነው። በመሆኑም ዘመኑ በአገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን፣ በዓለም ዐቀፍ ወጀቦችም የታጀበ ነው። በዚያ ላይ በ2012 የተከሰተው የኮቪድ ወረርሽኝ የዓለምን ኢኮኖሚ አናውጦታል። ዐቢይ የተወዳጇቸው የዩናይትድ አረብ ኤሚሬትስ መሪዎች ጨምሮ የመካከለኛው ምሥራቅ ሰዎችም አካባቢያዊ ተፅዕኗቸውን ያሳደጉበት ዘመን ላይ ነን። ኢትዮጵያም ደሴት አይደለችም፤ ዓለማችን መርከብ ከሆነች እና ወጀብ ከመታት አብራ ትናጣለች። ከዓለም ዐቀፍ ትርምሶች ታተርፋለችም፣ ታጎድላለች።

 

ይህ በእንዲህ እያለ፣ እስራኤል እና አሜሪካ ኢራን ላይ ጦርነት ሲያውጁ፣ የአውሮፓ የኢትዮጵያ ተንታኞች (Ethiopia experts) ‘ዐቢይ ይህንን አጋጣሚ ከለላ አድርገው ኤርትራ ላይ ጦርነት ያውጃሉ’ በማለት ተነበዩ። ይህንን የተነበዩት በብዙ ምክንያቶች ነው። አንደኛ፣ ዐቢይ በነውጥ ቀዛፊ ስለሆኑና፣ ከነውጥ ውስጥ ጥቅማቸውን ፈልቅቀው እንደሚያወጡ እርሳቸውም የማይደብቁት ጉዳይ በመሆኑ  ነው። በቅርቡ እንኳን በዓለም ዙሪያ ስላንዣበበው የግጭት አደጋ ሲጠየቁ እኛ የሚጠበቅብን ከግጭቶቹ ውስጥ ዕድል (opportunity) ፈልቅቀን ማውጣት ነው ብለው ነበር። ሁለተኛ፣ ዐቢይ የትግራይ ጦርነት በሥምምነት ሲቋጭ ከተኳረፏቸው የኢሳያስ አፈወርቂ መንግሥት ጋር እሰጥ አገባ ውስጥ ገብተዋል፤ ይኸውም የባሕር በር ጥያቄን ግንባር ቀደም የውጭ ጉዳይ ፖሊሲያቸው አጀንዳ አድርጎታል። ምንም እንኳን የባሕር በር የምናመጣው “በሰላም ነው” እያሉ ቢዝቱም ማንም አላመናቸውም። ጉዳዩን በሰላም ለማድረግ ብዙ ዲፕሎማሲ የሚጠይቅ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን እርሳቸው ኃይልን እንደ ሁነኛ የችግር መፍቻ መንገድ ይመለከቱታል ተብሎ ስለሚታመን ነው - ተንታኞቹ እንዲህ ማሰባቸው። ሦስተኛ፣ የትግራይ ጦርነት የጀመረው ልክ የአሜሪካ ምርጫ የተካሔደበት ቀን ስለሆነ፣ የዓለም ትኩረት አቅጣጫ ሌላ ሰፈር ሲሆን፣ ዐቢይ አሕመድ የሆነ ነገር ያደርጋሉ ብለው ገምተው ነው። ነገር ግን ትንቢታቸው አልሠራም። 


የኢራን ጦርነት ከጀመረ ከሁለት ሦስት ቀናት በኋላ ተንታኞቹ “ትንቢታቸው ለምን እንዳልሠራ” በመተንተን ፈንታ፣ ዐቢይ አሕመድ ለምን ጦርነቱን እንዳልጀመሩ ለመተንተን ሞክረዋል። ዐቢይ አሕመድ እንኳን በአስተርጓሚ እገዛ እና በእንግሊዝኛ ዜና መነፅር የሚመለከቷቸውን ሰዎች ቀርቶ እኛ በየቀኑ የሚሠሩትን እያየን፣ የሚናገሩትን እያደመጥንም ቢሆን ለትንታኔ ያስቸግሩናል። እዚህ ጋር ተንታኞቹ የሠሩት አንዱ ስህተት ዐቢይ አሕመድ ራሳቸው እንደተናገሩት ከግጭቶች ጥቅም ፈልቅቀው ያወጣሉ፤ ለፖለቲካ ዓላማቸው የትኛውንም አካል ወደ ነውጥ ይገፋሉ። ነገር ግን ግጭቶችን ራሳቸው እንደሚጀምሩ አንድም ማስረጃ የለንም። የምዕራብ ተንታኞች ከገመቱት በተቃራኒው የትግራይን ጦርነት ሁለቱም ወገኖች በትርዒት እና ፉከራ ሲቀሰቅሱት ቆይተው፥ የመጀመሪያውን ጥይት የተኮሱት ራሳቸው ሕወሓቶች ናቸው። ከዚያ አስቀድሞ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነሠ) እና መንግሥት መካከል ውጊያ የተጀመረው በራሱ ትጥቅ አልፈታም ብለው ባመፁ የኦነሠ አባላት ነው (ኦነግ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ የነበረውን ስምምነት ዝርዝር ባይታወቅም፣ በአንድ አገር ውስጥ ቅቡልነት ያለው ታጣቂ ኃይል መንግሥት ብቻ መሆኑን መከራከር አንችልም)። በፋኖ እና በመንግሥት መካከልም የተጀመረው ጦርነትም መነሻው ልዩ ኃይል መፍረስ የለበትም ብለው ባመፁ የፋኖ ታጣቂዎች ነው። ጦርነቱን ዐቢይ ናቸው ያወጁት ተብሎ ብዙ ክርክር ሊነሳ ይችላል። ነገር ግን እርግጡ ነገር ከሁሉም ግጭቶ እርሳቸው ሥልጣናቸውን ከትላንት የተሻለ ዛሬ ለማደላደያነት እንደተጠቀሙባቸው ብቻ ነው። 


አንድ የእንግሊዝ ዲፕሎማት ዐቢይ ወደ ሥልጣን የመጡ ሰሞን የተሰማቸውን ለተመራማሪዎች እንደተናገሩት፣ “Abiy was a disruptor… He was changing everything all the time… Ethiopians couldn’t keep up; we could not keep up.” (“ዐቢይ ማርሽ ቀያሪ ናቸው። … ሁሌም ሁሉንም ነገር እየቀያየሩት ነበር።… ኢትዮጵያውያንም በሳቸው ፍጥነት ምን እያደረጉ እንደሆነ ማወቅ አልቻሉም፣ እኛም አልቻልንም።” ዓይነት ነገር) ብለው ነበር። በዚህም “የነውጥ ቀዛፊው” ዐቢይ አሕመድ እስከ የሰላም ኖቤል ተሸላሚነት ደርሰዋል።  


ዐቢይ አሕመድ ነገሮችን በማይታመን ፍጥነት ማድረግ ይወዳሉ። ወደ ሥልጣን የወጡ ሰሞን በየቀኑ ሰበር ዜና ይሰጡን ነበር፤ አንዱን አውርተን ስንጨርስ ሌላኛው ይቀጥላል። በዚህ መሐል እርሳቸው ሥራቸውን ይሠራሉ፤ አንድም ሰው ከሰበር ዜና ጠለቅ ብሎ የድርጊቶቻቸውን እና የውሳኔዎቻቸውን ዘላቂ ጦስ መተንተን አልቻለም፤ ቢችልም አድማጭ የለውም። ብዙዎቻችን መለስ ብለን ስናስታውሰው፣ ባለፉት ስምንት ዓመታት እየታመስን የተንገረገብነው ብዙ ጊዜ ነው። አሁን ማን ይሙት፣ በ2014 ከጦር ሜዳ ሆነው እንዲያ ሲያብጠለጥሏቸው የነበሩት ጌታቸው ረዳ የመንግሥታቸው ሹመኛ እና ተከላካይ ይሆናሉ ብሎ ማን አሰበ? በርካታ የሕወሓት ሹመኞች የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት ሊሆኑ ሲሻሙ እርሳቸው ግን ለምን ጌታቸውን መረጡ? ጌታቸው ላይ የሕወሓት አንጋፋ አባላት ሲያምፁ እርሳቸው ለምን ቀጥተኛ ጣልቃ ሳይገቡ ቀሩ? ምን አስበው ነበር? አሁንስ ምን እያሰቡ ነው?


የኮሪደር ልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ጀምረዋል። ለነዚህ የልማት ሥራዎች በርካታ መኖሪያ ቤቶች መፍረስ እና ነዋሪዎች እንዲነሱ ተደርጓል። ይህን ሲያደርጉ የሚያደርጉበት ፍጥነት እና ስፋት ሁሉም ሰው ከአቅሙ በላይ (overwhelming) ይሆንበት ነበር። የተፈናቃዮቹ ዕጣ ፈንታ ሳይወራ፣ አዲስ የሚመረቁት ሰፈሮች ይመጣሉ፤ በዚሀ መሐል ሌላ ሰፈር ይፈርሳል። በአንድ በኩል ብዛቱ፣ በሌላ በኩል ፍርሐቱ፣ በዚያ ላይ ፓርቲያቸው ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ያሠማራቸው ካድሬዎች የሚነዙት ፕሮፓጋንዳ! ሁሉም ይህንን በሚያህል ስፋት እና ጥልቀት የሚሠራ ሥራ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እና ጦስ ሳይተነን እንዲያልፍ እያደረጉ ነው። 


ዐቢይ አሕመድ ጠላቶቻቸውን ሲችሉ የእርሳቸው ተከላካይ ጠበቃ፣ አልያም አቅመ ቢስ ያደረጉበት መንገድ የማይታመን ነው። ኢሳትና ኦኤምኤን የተባሉ ቴሌቪዥኖች በአንድ ወቅት አገር አንቀጥቅጥ እንዳልነበሩ፣ ዛሬ ተከፋፍለው እና ተመናምነው የከሸፉበት ጥበብ አልተተነተነም። ተቃዋሚ ፓርቲዎች ወደ አጋር ፓርቲነት የተቀየሩበት መንገድ ከተራ በሹመት ማባበል በላይ መመርመር አለበት። ማኅበራዊ ሚዲያን ከተቃዋሚዎች መድረክነት ወደ ገዢው ፓርቲ ካድሬዎች መፈንጫነት የቀየሩበት መንገድም አልተስተዋለም። ምክንያቱም ይህን ሁሉ ለመመርመር ጊዜ አልሰጡንም። እንደ አስማተኛ ማስቀየሻ ሰበር ዜናዎች አሏቸው፤ ይኼን ብልጭልጭ አይተን ዞር ስንል ያኛው ሔዷል። 


“ሐሳብ አመንጪው” ጠቅላይ ሚኒስቴር


ባለሥልጣኖቻችን አዳዲስ የመንግሥት ሥራዎችን ሲያስተዋውቁ “በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሐሳብ አመንጪነት” ብለው ይጀምራሉ። እኔና አንድ ጓደኛዬ፣ የኢቢሲ የቴሌግራም ዜና ዘገባዎች ላይ ባደረግነው ቀላል ሐሰሳ፣ በጠቅላይ ሚኒስትሩ “ሐሳብ አመንጪነት” የሚለው 14 ዜናዎች  ውስጥ፣ በጠቅላይ ሚኒስትሩ “አነሳሽነት” የሚለው ደግሞ 10 ዜናዎች ውስጥ ከነሐሴ 2012 ጀምሮ መጠቀሱን አስተውለናል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሐሳብ አመንጪነት የተጠቀሱት በብዛት ከኮሪደር ልማቱ ጋር በተያያዘ ቢሆንም፣ ከአረንጓዴ አሻራ፣ ከኢቢሲ እድሳት፣ ከክብረ በዓሎች ዝግጅት፣ ከተቋማት መመሥረት፣ እና ከስታዲየም ግንባታዎች ዕቅድ ጋር በተያያዘ ተወድሰዋል። 


እርግጥ ነው ብዙ ከከተማ ማስዋብ ፕሮጀክቶች ጋር የተያያዙት ሥራዎች በእርሳቸው ፍላጎት ባይሆን አይሠሩም፣ ቢሠሩም አሁን በሚሠሩበት ፍጥነትና ስፋት አይከናወኑም ነበር። የሹማምንቱና የዘገባዎቹ አጠቃቀም ግን ዕውቅና ከመስጠትም በላይ ሰበብ እየፈለጉ የማወደስ ዓይነት ይመስላል፤ እንደሚመስለኝ የሹመት መንገዱ ታማኝነትን በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ማረጋገጥ ነው። ሹማምንቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ሳይጠቅሱ መናገር 'ክሬዲቱን’ እንደመውሰድ እንዳይቆጠርባቸው ሰግተው፣ አልያም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልካም ሥራዎች እና አፈፃፀሞች ላይ ካልተጠቀሱ ቅር ይላቸዋል በሚል ፍራቻ (ወይም ቅር እንደሚላቸው ከዚህ ቀደም ስላስተዋሉ) ሊሆን ይችላል። ያም ሆነ ይህ አገሩ ውስጥ ሰው የሌለ ይመስል ሁሉንም ነገር ጠቅልሎ ለአንድ ሰው መስጠት አሳሳቢ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እውነትም ዜናዎቹ እና ሹማምንቱ እንደሚሉት የሁሉም ነገሮች ሐሳብ አመንጪ ከሆኑም አደገኛ ነው፤ ምክንያቱም ተደጋግሞ እንደተባለው ጠቅላይ ሚኒስትሩ አገራችንን በራሳቸው አምሳል መልሰው እየሠሯት ነው። እውነታቸውን ካልሆነና እየሸነገሏቸውም ከሆነ ያው ለራሳቸውም ቢሆን አደገኛ ነው።


ለንፅፅር እንዲረዳን፣ ትራምፕ የካቢኔ አባሎቻቸውን ሰብስበው ምስጋና ሲቀበሉ የሚያሳዩ ቪዲዮዎች አሉ። ይህ ለምን ሆነ ብዬ የተሰጡ ትንታኔዎችን ወዲያ ወዲህ እያልኩ ሳፈላልግ በርካታ መልሶች ተመለከትኩ። አንዳንዶቹ ታማኝነታቸውን ለማረጋገጥ ነው፣ ሌሎቹ ትራምፕ መወደስ እንደሚወዱ ስለሚያውቁ ሊያባብሏቸው ነው፣ ከፊሎቹ ትችት የበዛባቸውን የፕሬዚዳንቱን ሞራል ለመጠበቅ ነው፣ ቀሪዎቹ ደግሞ በተቀናቃኞቻቸው የተበላሸውን ገጽታቸውን ለመገንባት ነው የሚል ትንታኔ ሰጥተውበታል። የኛም ሹማምንት እነዚህን የ'ክሬዲት' ስጦታዎች የሚያዥጎደጉዱት ከነዚህ ምክንያቶች በተለየ ምክንያት ይሆናል ብዬ አልገምትም። ሆኖም፣ በአንድ ነገር መስማማት እንችላለን፤ እንዲህ ያለ የቁልምጫ እጅ መንሻ የሚጠብቀው አምባገነናዊ ማንነት ያለው የመንግሥት ሹመኛ ብቻ መሆኑን ነው። 


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በራሳቸው “ሐሳብ አመንጪነት” ኢትዮጵያን በራሳቸው ፍላጎት ልክ መልሰው ለመሥራት ቆርጠዋል ይባላል (የቶም ጋርድነር መጽሐፍም በዚሁ ዙሪያ ነው የሚያጠነጥነው)። ጦርነት እና ግጭት ቢፈነዳ፣ ትችት እና ማስፈራሪያ ቢዘንብ ማንንም የሚሰሙ አይመስሉም። የሚፈልጉትን ያደርጋሉ። “ታላቁ ትርክት” በሚል ርዕስ ለኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን የጋራ ትርክት ለመፍጠር ትርክቱንም ተቀባይነት እንዲያገኝ ለማድረግ እየሞከሩ ነው። አገራዊ ምክክሩን በመጠቀም እስከ ሕገ መንግሥት ክለሳ ለመድረስ ይሞክራሉም ተብሏል። መሐል አዲስ አበባን የዛሬ ስምንት ዓመት ያያት ሰው ዛሬ ገብቶ አይወጣባትም። የምኒልክ ቤተ መንግሥትን በከፊል ቀይረው ዩኒቲ ፓርክ ያሰኙት ሰሞን ለውጡ ከቢሮዬ ጀምሮ አገር ያዳርሳል ብለው ነበር። እንዳሉትም፣ በቤተ መንግሥቱ ዙሪያ ያሉት ሰፈሮች ሁሉ ተቀይረዋል። አዲስ ቤተ መንግሥትም ከተማዋ አናት ላይ እየተሠራ ነው። በየከተማዎቹ አዲስ አበባ የሚሠራው ዓይነት የመንገድ ዳርቻዎችን የማስጌጥ ሥራ እንዲባዛ ትዕዛዝ ተሰጥቷል፣ እየተሠራም ነው (“የኮሪደር ልማት” የተሰኘው የከተሞች ዕድሳት ቢያንስ በ54 ከተሞች እንደተከናወነ ሰምቻለሁ፤ ወደ ገጠርም እየዘለቀ እንደሆነ የሚያሳዩ ጅምሮች በደቡብ ኢትዮጵያ አሉ)። በግለሰብ ባለቤትነት የሚተዳደሩ ሕንፃዎች ቀለም ላይ ሳይቀር፣ የግድግዳው እና መስታወቱ ዓይነት ላይ ጭምር መንግሥታቸው የራሱ ምርጫ አለው። 


የኮሪደር ልማቱ ብዙ ወጪ ይጠይቃል። ኢትዮጵያ ደግሞ በግጭቶቹም፣ በኮቪድም፣ በዓለም ቀውስም፣ በፊስካል ፖሊሲ ለውጥም ከፍተኛ የዋጋ ንረት እየፈተናት ነው። እርሳቸው ሥልጣን ላይ ሲወጡ ሃያ ምናምን ብር የነበረው አንድ ዶላር፣ ዛሬ በባንክ መቶ ሃምሳ ምናምን ገብቷል። የደሞዝተኛ ዜጎች ገቢ በአንድ ዓመት ውስጥ በግማሽ እንደቀነሰ ቁጠሩት። ስለዚህ የኮሪደር ልማቱ አስፈላጊ ቢሆን እንኳን “ኢትዮጵያ እነዚያን ሁሉ ነዋሪዎች የማፈናቀል፣ መልሶ የማቋቋም አቅም አላት ወይ? አዲሶቹ ግንባታዎች እና በተለይ ረብጣ ሀብት የሚፈስባቸው ባለመብራት የውሃ ፏፏቴዎች የሚጨምሩ መዝናኛ ሥፍራዎችን የመሥራት አቅም አላት ወይ? ሰላምና መረጋጋት ሳይኖር ከከተሞች ርቀው የተሠሩት ቅንጡ ሪዞርቶች የሚያርፉባቸው ቱሪስቶች ይኖራሉ ወይ? የወጡባቸውን ወጪዎች ይመልሳሉ ወይ? ዘላቂ የገቢ ምንጭ ይሆናሉ ወይ?” የሚል ጥያቄ ቢነሳ የሚያስቀይም አይሆንም።  ሆኖም፣ ቀድም ብዬ እንዳልኩት ዐቢይ አሕመድን ከመንገዳቸው ማንም፣ ምንም አያስቆማቸውም።


የጫካ ፕሮጀክት የሚባለውን ቤተ መንግሥት የሚጨምር “ሳተላይት ከተማ” በአዲስ አበባ  አንድ አናት ላይ ሲገነቡ፣ ከ500 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚወስድ ተናግረዋል። የልማት ተነሺዎች ተበደልን ብለው ፍርድ ቤት መሔድ የሚችሉበት መንገድ ቀጭን ነው። ሕልማቸውን የሚያከናውኑት ከሕዝባቸው ጋር ተማክረው አይደለም። ለልጆቹ የሚበጀውን እንደሚያውቅ አባት የሕዝባቸውን ጫጫታ መስማት አይፈልጉም። ከዚህ በፊት ፓርላማው ገንዘብ ላልሰጠኝ የጫካ ፕሮጀክት ምንም ሊጠይቀኝ አይችልም እስከማለት ደርሰው ነበር። ጄኔራል ኦዲተሯ ባንድ ወቅት የነዚህ "ሜጋ" (ግዙፍ) ፕሮጀክቶች በጀት በገንዘብ ሚኒስቴር በኩል ስላማያልፍ ኦዲት የማድረግ ሥልጣን የለንም ሲሉ ሰምቻለሁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚፈልጉትን የሚያሳኩት በእንዲህ ያለ ከሕግ የበላይነት ጭምር ነው።


ባለፉት ስምንት ዓመታት ያየነው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጉዞ፣ የማይታመን ጥድፊያን ከማይታመን የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ነውጥ ጋር አጣምሮ የያዘ ነው። ዐቢይ አሕመድ ኢትዮጵያን በራሳቸው ምስል እና ምናብ ልክ ለመቅረጽ ሲተጉ፣ የዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ፣ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታ እና የሕግ የበላይነት ግን የዚሁ “ፈጣን ጉዞ” ሰለባ ሆነዋል። ዐቢይ ወደ ሥልጣን የወጡት በሰላማዊ ሒደት ቢሆንም፣ እንደ ቀደምት መሪዎች ሁሉ መሰንበቻቸው በነውጥ ሆኗል።  የነገዋ ኢትዮጵያ ዕጣ ፈንታም የሚወሰነው የተዋቡ የከተማ ኮሪደሮችና ወንዞች በዚህ በኩል፣ ጦርነትና የኑሮ ውድነት በወዲያ በኩል በሚያፈሩት ፍሬና በሚያስከትሉት ጦስ መካከል ነው። ስምንት ዓመታት አንድ የአሜሪካ ፕሬዚደንት ሁለት ጊዜ ተመርጦ አገልግሎቱን የሚያጠናቅቅበት ዘመን ነው። የእርሳቸው ሥልጣን ግን ገና እየጀመረ ይመስላል። ጥሩፋታቸውን ይኼ ነው ብሎ መተንበይ ይቸግራል። ነገር ግን በሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ፣ በሕግ የበላይነት፣ በዴሞክራሲ እና መልካም አስተዳደር መልካም ሥም ጥለው ያልፋሉ ብሎ ለመገመት ምልክቱ የለም። የነውጦቹ መቋጫም ምን እንደሚሆን መገመት ነብይነት ይጠይቃል። ዐቢይ አሕመድ ፈረንጆቹ እንደሚሉት “he has won the battles but not the war” (“ጦር ሜዳው ላይ ቀንቷቸዋል፤ ጦርነቱን ግን አላሸነፉም” እንደማለት።) 


መጪውን አብረን የምናየው ይሆናል፣ ነገር ግን ትልቁ ጥያቄ “ቀጣዩ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዕቅድ ምንድን ነው?” የሚለው ሳይሆን፣ “ኢትዮጵያውያን ይህንን ሁሉ ነውጥ፣ የኢኮኖሚ ጫና እና ያልተገደበ ሥልጣን እስከመቼ ተሸክመው መዝለቅ ይችላሉ?” የሚለው ነው።

3 comments:

  1. መጪውን አብረን የምናየው ይሆናል፣ ነገር ግን ትልቁ ጥያቄ “ቀጣዩ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዕቅድ ምንድን ነው?” የሚለው ሳይሆን፣ “ኢትዮጵያውያን ይህንን ሁሉ ነውጥ፣ የኢኮኖሚ ጫና እና ያልተገደበ ሥልጣን እስከመቼ ተሸክመው መዝለቅ ይችላሉ?” የሚለው ነው።
    This is the point !!!

    Reply
  2. ኢ መደበኛ ሃይል ብለው የመጀመሪያውን ቃታ የሳቡት እሳቸው አይደሉም ወይ? ሌላው ፅሁፍ ማለፊያ ነው። ፅሁፉ ያነጋግራል፣ ከራስ ህሊና ጋር ሙግት ያስገጥማል።

    Reply
  3. በየዓመቱ መጋቢትን ጠብቀህ መጻፍህ ለአንባቢያን በበጎ ጎኑ የሚታይ ነው ምን አልባትም የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እንደ በቀልተኛዎቹ ህወሓቶች ወደ ቃሊቲ እስር ቤት እንደጨመሩህ አላደረጉብህም (የተሻለ ነጻነት ሰላለ) ሆኖም ግን የየአውደ ዓመታቱ ጽሁፎችህ Smeared biography እየሆኑ እስከመቼ ይቀጥላሉ? የሚለው ጥያቄ እንደ ተደራሲ ያሳስበኛል ። በበቂ ሁኔታ ያልተተነተኑ በማህበራዊ ሚዲያ በየዕለቱ ተቃርኖ ያላቸው ሰዎች ከሚያነሱት የተለየ ካልሆነ scrolled ሆኖ ማለፉ አያጠራጥርም

    Reply

Wednesday, April 1, 2026

The Bathsheba Syndrome in Ethiopian Politics: Power, Hubris, and the Crisis of Restraint

The Bathsheba Syndrome in Ethiopian Politics: Power, Hubris, and the Crisis of Restraint

Introduction

The concept of the Bathsheba Syndrome—derived from the biblical story of King David—captures a recurring pathology of leadership: the moral and strategic decline that follows success, power, and insulation from accountability. In the Ethiopian political context, this syndrome offers a compelling analytical lens through which to interpret cycles of elite overreach, institutional erosion, and recurring instability.

Ethiopian politics, shaped by imperial legacies, revolutionary centralism, and ethnic federalism, has repeatedly produced leaders whose greatest vulnerability is not weakness, but unchecked strength

Power Without Restraint

In Ethiopia, political authority has often been personalized rather than institutionalized. Leaders, once consolidated in power, tend to operate within closed circles where dissent is minimized and loyalty is rewarded. This creates the classic conditions of the Bathsheba Syndrome:

Overconfidence following political victory

Erosion of internal checks and balances

Moral exceptionalism in decision-making

Whether under imperial rule, the Derg military regime, or the post-1991 federal order, leadership has frequently drifted toward centralization once legitimacy is secured. The transition from reformist promise to authoritarian tendency is not accidental—it is structural.

The Illusion of Invincibility

One of the defining features of the syndrome is the belief among leaders that they are indispensable. In Ethiopia, this has manifested in:

The marginalization of opposition voices

The weakening of independent institutions

The conflation of state survival with regime survival

Such tendencies create a political environment where leaders interpret criticism as threat rather than correction. Consequently, policy errors are not acknowledged early; they are compounded.

This illusion of invincibility often leads to strategic miscalculations—particularly in matters of security, federal-regional relations, and national identity politics.

Federalism and the Expansion of Political Hubris

Ethiopia’s multinational federal system was designed to manage diversity and prevent domination. However, the Bathsheba Syndrome has affected not only federal elites but also regional political actors.

At both levels, power has sometimes been exercised with:

Selective interpretation of constitutional principles

Instrumental use of identity for political consolidation

Suppression of intra-group dissent

Thus, the syndrome is not confined to a single leader or party; it is diffused across the political class. Regional authorities, once empowered, may replicate the same patterns of overreach they once opposed at the center.

Strategic Miscalculation and National Consequences

The most dangerous outcome of the Bathsheba Syndrome is not merely ethical failure, but strategic misjudgment. In Ethiopia, this has contributed to:

Escalation of internal conflicts

Breakdown of trust between federal and regional actors

Militarization of political disputes

Weakening of national cohesion

Leaders operating under the illusion of control often underestimate the complexity of Ethiopia’s social fabric. Decisions made without consultation or humility tend to trigger unintended consequences, deepening fragmentation rather than resolving it.

The Absence of Corrective Mechanisms

A healthy political system contains mechanisms that prevent the syndrome from taking root: independent courts, free media, strong legislatures, and active civil society.

In Ethiopia, however, these mechanisms have often been fragile or politicized. As a result:

Errors are rarely corrected early

Accountability becomes reactive rather than preventive

Leadership operates in echo chambers

This institutional weakness allows the syndrome to persist across political transitions.

A Culture of Power Rather Than Service

At its core, the Bathsheba Syndrome reflects a deeper philosophical problem: the transformation of leadership from public service into personal entitlement.

In Ethiopia, political office is frequently perceived as:

A source of authority rather than responsibility

A platform for dominance rather than stewardship


This cultural dimension reinforces the structural conditions that enable ethical and strategic decline.

Conclusion: 

Toward Ethical and Institutional Renewal

The lesson of the Bathsheba Syndrome is both simple and profound:
power, when unchecked, becomes self-destructive.

For Ethiopia, overcoming this syndrome requires more than leadership change—it demands:

Strengthening constitutionalism and rule of law

Institutionalizing accountability beyond personalities

Encouraging political humility and dialogue

Reframing leadership as service, not supremacy


Ultimately, the stability of the Ethiopian state depends not on the strength of its leaders alone, but on their restraint. For history shows that the greatest threat to Ethiopian politics is not external pressure, but the internal failure of those entrusted with power to govern themselves.

Gulf Rivalries and the Reconfiguration of Security in the Horn of Africa and the Red Sea

 

Gulf Rivalries and the Reconfiguration of Security in the Horn of Africa and the Red Sea

Abstract

Over the past decade, rivalries among Gulf powers—principally between the and , alongside the involvement of , , and —have reshaped the geopolitical landscape of the Horn of Africa and the Red Sea basin. These rivalries, expressed through proxy engagements, economic investments, and strategic alignments, have transformed local conflicts into extensions of broader Middle Eastern competition. This article examines the structural drivers, operational modalities, and regional consequences of these rivalries, with particular focus on Sudan, Ethiopia–Eritrea tensions, and Somalia/Somaliland dynamics.


1. Strategic Drivers of Gulf Engagement

The Horn of Africa occupies a pivotal geostrategic position adjacent to the —one of the world’s most critical maritime corridors. Gulf states initially expanded their presence in the region in response to perceived Iranian influence, especially following the . Their objectives can be broadly categorized into three domains:

  • Maritime Security: Ensuring uninterrupted trade flows through the Red Sea.
  • Resource Acquisition: Access to agricultural land, minerals (notably Sudanese gold), and logistics corridors.
  • Geopolitical Competition: Countering ideological and strategic rivals, including Islamist movements and Iranian proxies.

However, intra-Gulf competition—intensified during the —transformed these engagements into zero-sum contests.


2. Competing Blocs and Modes of Influence

The rivalries in the Horn are structured around loosely defined blocs:

  • UAE محور (Axis): The UAE has pursued an assertive, often revisionist strategy, supporting anti-Islamist actors and leveraging military logistics, port infrastructure, and post- ties with Israel.

  • Saudi–Egypt محور: Saudi Arabia, frequently aligned with Egypt, emphasizes regime stability, Red Sea security, and the containment of Islamist networks such as the Muslim Brotherhood.

  • Qatar–Turkey محور: Qatar and Turkey tend to support Islamist-leaning or status-quo actors, combining financial aid, political backing, and in some cases drone capabilities.

These alignments are fluid rather than fixed, often shifting in response to evolving regional crises.


3. Sudan: A Theatre of Proxy Convergence

The ongoing exemplifies the convergence of Gulf rivalries. The conflict between the Sudanese Armed Forces (SAF) and the Rapid Support Forces (RSF) has been internationalized through external support:

  • The UAE has been widely accused (though it denies) of providing logistical and military support to the RSF.
  • Saudi Arabia and Egypt have leaned toward supporting or mediating alongside the SAF.
  • Iran has reportedly supplied drones to SAF elements, with logistical routes involving Eritrean ports such as Assab and Massawa.
  • Turkey and Qatar have also extended varying degrees of support to SAF-aligned actors.

This multiplicity of external patrons has entrenched a military stalemate, exacerbating humanitarian crises and fragmenting Sudan’s territorial integrity.


4. Ethiopia–Eritrea and Red Sea Geopolitics

Tensions between and have been increasingly influenced by Gulf alignments. UAE support for Ethiopian Prime Minister —particularly in economic and security domains—has intersected with Ethiopia’s ambitions for Red Sea access, including agreements with Somaliland.

Conversely, Saudi Arabia has cultivated closer ties with Eritrea, partly as a counterbalance to UAE influence. Eritrean ports, notably Assab and Massawa, have thus become critical nodes in both Gulf and Iranian strategic calculations, raising the risk of militarization along the Red Sea littoral.


5. Somalia, Somaliland, and Fragmented Sovereignty

In and Somaliland, Gulf rivalries intersect with fragile state structures:

  • Turkey and Qatar have supported the Somali federal government, including military training and infrastructure.
  • The UAE has engaged with Somaliland, particularly through port investments in Berbera.
  • The ’s recognition of Somaliland in December 2025 has been interpreted by some analysts as aligning with UAE strategic interests in securing Red Sea access.

These overlapping engagements complicate Somalia’s sovereignty and risk deepening fragmentation.


6. Broader Red Sea Militarization

The Red Sea is increasingly characterized by:

  • Expansion of foreign military bases.
  • Intensification of port diplomacy.
  • Proxy militia activity.

These dynamics intersect with Iranian influence and the activities of the , particularly in the context of escalating Iran–Israel–U.S. tensions. The Horn of Africa thus functions as both a logistical corridor and a strategic buffer zone in wider Middle Eastern conflicts.


7. Implications for Regional Stability

The consequences of Gulf rivalries in the Horn are profound:

  • Conflict Prolongation: External arms flows sustain military stalemates.
  • Humanitarian Crisis: Displacement, famine risks, and civilian casualties intensify.
  • Diplomatic Fragmentation: Competing external agendas undermine African Union and UN mediation efforts.
  • Economic Distortion: Infrastructure investments are often tied to patronage networks rather than inclusive development.

Moreover, shifting alliances—such as evolving Saudi–UAE relations—introduce unpredictability into an already volatile environment.


8. The Iran Factor and Future Trajectories

The broader confrontation involving Iran introduces both constraints and risks:

  • Short-term: Gulf states may reduce proxy engagement in the Horn to prioritize internal security.
  • Long-term: Iran may exploit governance vacuums, particularly through Eritrean or Sudanese corridors.
  • Maritime Risk: Escalation could disrupt Red Sea shipping, with global economic implications.

Conclusion

Gulf rivalries have effectively reconstituted the Horn of Africa as an extension of Middle Eastern geopolitics. While these engagements have brought investment and strategic attention, they have more often intensified conflicts, undermined local governance, and complicated peacebuilding efforts.

Sustainable stabilization requires a recalibration of external involvement—prioritizing coordinated diplomacy, African-led mediation frameworks, and development-oriented investment. Sudan remains the critical test case: without a cessation of external military support to both SAF and RSF, the risk of a broader Red Sea conflagration will persist.

In this evolving geopolitical theatre, the Horn of Africa is no longer peripheral; it is central to the future architecture of regional and global security.

Tuesday, March 10, 2026

The 17 Century British Revolutions and Its contributions to Modern Democracy.


The Glorious Revolution (1688–1689)

The was a pivotal political event in English history that resulted in the overthrow of the Catholic monarch and the establishment of a constitutional monarchy under and .

Background

During the late seventeenth century, tensions grew in England over religion and political authority. King James II, a Catholic ruler in a predominantly Protestant country, attempted to expand royal power and promote religious tolerance toward Catholics. Many members of the English political elite feared that he intended to establish an absolute monarchy similar to those in continental Europe.

The crisis deepened in 1688 when James II’s wife gave birth to a Catholic heir, raising concerns that a Catholic dynasty would permanently rule England. In response, a group of Protestant nobles secretly invited William of Orange—Mary’s husband and the Dutch Protestant leader—to intervene.

The Revolution

In November 1688, William landed in England with a military force. Facing widespread opposition and desertion within his army, James II fled to France. Because the transition of power occurred with relatively little bloodshed, it became known as the “Glorious Revolution.”

Consequences

The revolution fundamentally transformed the English political system. In 1689, Parliament enacted the , which limited the powers of the monarchy and strengthened parliamentary authority. It guaranteed regular parliaments, free elections, and protections against arbitrary royal rule.

Historical Significance

The Glorious Revolution established the principle of constitutional monarchy, where the monarch rules according to laws approved by Parliament. It also strengthened the foundations of modern liberal democracy and influenced later political developments, including constitutional thought in Europe and North America


Oliver Cromwell and the Earlier English Revolution

Oliver Cromwell was not involved in the Glorious Revolution, because he had died in 1658—about thirty years earlier. However, he was the central figure of an earlier revolutionary period in English history.

Cromwell’s Revolution

Cromwell rose to prominence during the English Civil War. This war was fought between supporters of Parliament and the forces of King Charles I. Cromwell became the most successful military commander of the parliamentary army, particularly through the creation of the New Model Army.

After Parliament’s victory, Charles I was tried and executed in 1649. England then abolished the monarchy and became a republic known as the Commonwealth of England.

Cromwell as Lord Protector

In 1653, Cromwell assumed power as Lord Protector, effectively ruling as a military-backed leader. His government pursued strict Protestant policies and suppressed uprisings in Ireland and Scotland.

Connection to the Glorious Revolution

After Cromwell’s death, political instability led to the restoration of the monarchy in 1660 under Charles II. The tensions between monarchy and Parliament continued, eventually culminating in the Glorious Revolution of 1688.

Historical Significance

Cromwell’s revolution challenged absolute monarchy and demonstrated that a king could be overthrown. The later Glorious Revolution built on these earlier struggles by establishing a constitutional monarchy, balancing royal authority with parliamentary power.

Contributions of the English Civil War and the Glorious Revolution to Modern Democracy

Two major political upheavals in England—the English Civil War and the Glorious Revolution—played decisive roles in shaping the foundations of modern democratic governance. Together they transformed the relationship between rulers, institutions, and citizens.

1. Limitation of Absolute Monarchy

The English Civil War challenged the doctrine of the divine right of kings, which had justified absolute monarchy. The execution of Charles I demonstrated that rulers could be held accountable to the law and to political institutions. This marked a historic shift toward the principle that government authority must be limited.

2. Emergence of Parliamentary Sovereignty

Both revolutions strengthened the authority of Parliament. During the Glorious Revolution, William III and Mary II accepted the English Bill of Rights, which established that the monarch could not suspend laws, raise taxes, or maintain a standing army without parliamentary consent. This principle laid the groundwork for parliamentary sovereignty.

3. Development of Constitutional Government

The settlement after 1689 created one of the earliest examples of constitutional monarchy, where political authority is exercised according to established laws and institutional checks. This concept became a cornerstone of modern democratic systems.

4. Protection of Civil and Political Rights

The English Bill of Rights introduced key democratic protections, including regular parliaments, free elections, and the right to petition the government. These principles later influenced other democratic documents such as the U.S. Bill of Rights and many constitutional systems worldwide.

Historical Legacy

Together, these revolutions helped establish the central democratic ideas that governments must be limited, accountable, and governed by law. Their legacy shaped political developments in Britain, North America, and eventually many constitutional democracies across the modern world.

 Important political thinkers lived during the period of the English Civil War and the Glorious Revolution. 

Their ideas helped shape modern political philosophy and democratic theory.

1. Thomas Hobbes (1588–1679)

Hobbes lived through the English Civil War and was deeply influenced by the chaos of political conflict. In his famous book Leviathan, he argued that humans naturally live in a condition of conflict and insecurity. To avoid disorder, people form a social contract and grant authority to a strong sovereign state. Although Hobbes supported strong government, his theory introduced the modern concept that political authority originates from the people.

2. John Locke (1632–1704)

Locke was one of the most influential thinkers of the Glorious Revolution. In Two Treatises of Government, he argued that governments exist to protect natural rights—life, liberty, and property. If rulers violate these rights, citizens have the right to resist or replace them. Locke’s ideas strongly influenced modern liberal democracy and later inspired the American and French revolutions.

3. James Harrington (1611–1677)

Harrington wrote The Commonwealth of Oceana, which proposed a republican system based on balanced political power, property distribution, and civic participation. His work contributed to early republican political thought.

4. Algernon Sidney (1623–1683)

Sidney defended the idea that sovereignty ultimately belongs to the people. His work Discourses Concerning Government criticized absolute monarchy and supported republican government.

Historical Importance

These thinkers helped develop key political concepts such as social contract theory, constitutional government, natural rights, and popular sovereignty, which remain foundational principles of modern democratic systems.

Sunday, February 15, 2026

Recognition, Resistance, and the Red Sea Chessboard — What Comes Next After the AU Rebuke?


Recognition, Resistance, and the Red Sea Chessboard — What Comes Next After the AU Rebuke?

The Horn of Africa has once again become the stage for a high-stakes geopolitical confrontation. Israel’s reported refusal to recognize the authority of the Federal Government in Mogadishu—paired with its deepening engagement with Somaliland—has collided directly with the African Union’s unusually forceful declaration defending Somalia’s sovereignty and territorial integrity. The result is not merely a diplomatic disagreement; it is the opening phase of what could become a prolonged strategic contest involving global powers, regional actors, and the future architecture of African borders.

At its Thirty-Ninth Ordinary Session in Addis Ababa, the African Union did more than issue a routine statement. It invoked foundational doctrines dating back to the Organization of African Unity: the inviolability of inherited borders and the collective defense of member-state sovereignty. By condemning Israel’s unilateral recognition of Somaliland and calling it “null and void,” the AU signaled a rare institutional cohesion. Historically cautious and often divided, the Union appears determined to prevent any precedent that could encourage separatist claims across the continent—from the Sahel to Central Africa.

Yet Israel’s calculus is unlikely to be reversed by declaratory diplomacy alone. For Israel, the Red Sea corridor is not peripheral—it is strategic lifeblood. Maritime routes connecting the Mediterranean to the Indian Ocean carry enormous commercial and security significance. Partnerships along this corridor offer intelligence advantages, logistical access, and geopolitical leverage against hostile actors operating in adjacent theaters such as Yemen. From a purely realist perspective, Somaliland presents itself as a comparatively stable coastal partner in an otherwise fragile region.

This divergence reveals the deeper fault line: Africa is asserting a legal and normative order, while external powers are operating within a framework of strategic pragmatism.

Possible Scenario One: Diplomatic Containment

The most immediate outcome may be a coordinated African diplomatic campaign aimed at isolating the recognition decision. AU member states could leverage multilateral platforms—particularly the United Nations—to reinforce Somalia’s territorial claims. If major African economies align behind this position, Israel may face growing political costs, even if practical cooperation with Somaliland continues quietly.

However, containment would require unusual African unity. Any fractures—especially among strategically located states—would weaken the AU’s position and embolden external actors.

Scenario Two: Strategic Polarization in the Horn

A more consequential trajectory would see the Horn drifting into competing geopolitical camps.

One axis could coalesce around Somalia’s recognized government, supported by AU mechanisms and potentially backed by partners wary of border revisionism. Another axis might quietly deepen ties with Somaliland, driven by maritime security interests, port access, and intelligence cooperation.

Such polarization would not necessarily produce open conflict, but it could harden rival security alignments—transforming the Red Sea basin into a theater reminiscent of Cold War–style influence politics.

Scenario Three: The Precedent Anxiety

The African Union’s unusually sharp language reflects a broader fear: precedent contagion.

If Somaliland’s recognition were normalized, other long-frozen territorial questions could resurface. Governments confronting internal insurgencies would interpret recognition as a threat to their own territorial permanence. Investors, too, tend to retreat from regions where borders appear negotiable.

In this sense, the AU is not reacting only to Somalia’s predicament—it is defending the structural stability of the African state system itself.

Scenario Four: Quiet De-escalation

Despite the rhetoric, diplomacy often advances through ambiguity. Israel could maintain practical cooperation with Somaliland while softening public posture, avoiding further symbolic steps that provoke continental backlash. Meanwhile, back-channel dialogue between Mogadishu and its partners might seek confidence-building measures rather than escalation.

Such calibrated ambiguity has precedent in international politics: relationships deepen without formal recognition, allowing all parties to claim partial victory.

The Strategic Lesson

Beyond immediate scenarios lies a larger transformation. Middle powers and regional organizations are increasingly willing to contest the actions of technologically and militarily stronger states when foundational norms are perceived to be at risk. Africa, long treated as an arena for external competition, is signaling a desire to shape the rules rather than merely react to them.

For the Horn of Africa, the stakes are especially high. The region sits astride one of the world’s busiest maritime arteries. Any sustained confrontation—diplomatic or military—would ripple far beyond Somalia, affecting trade flows, energy routes, and global security calculations.

What to Watch

Three indicators will reveal the trajectory ahead:

Whether additional states follow Israel’s lead—or explicitly reject it.

The durability of African Union cohesion once the immediate diplomatic moment fades.

The reaction of major global powers, whose silence or engagement will quietly tilt the balance.


Conclusion

This episode is not merely about recognition; it is about the evolving grammar of sovereignty in the twenty-first century. The African Union has drawn a firm normative line. Israel has demonstrated strategic resolve. Between them lies a region historically vulnerable to external rivalries yet increasingly conscious of its collective agency.

The coming months will test whether law or leverage proves the more durable currency in the Red Sea chessboard. What is certain, however, is that the Horn of Africa is no longer a peripheral arena. It is fast becoming one of the defining geopolitical crossroads of our time.

"State of Israel
The Office of the Prime Minister

February 14, 2026

To: The Office of the President of the Federal Government of Somalia

To Whom It May Concern,

The State of Israel acknowledges receipt of your communication dated February 6, 2026.

After careful consideration, we wish to clarify that we do not recognize the current administration in Mogadishu as the effective governing authority over the regions relevant to our strategic interests. Consequently, we decline the proposal to engage in formal diplomatic relations or strategic cooperation at this time.

Furthermore, we wish to emphasize that our focus and regional engagement remain centered on our existing relationship with Somaliland. We recognize Somaliland as a stable and reliable partner with whom we maintain a constructive and ongoing dialogue regarding security and regional cooperation.

Based on these facts, we are not seeking any alternative channels or agreements regarding the territories in question.

Sincerely,
The Office of the Prime Minister
State of Israel"

A structured analytical breakdown of the letter’s core accusations and strategic messaging. I will focus on political signaling, diplomatic framing, and implied objectives rather than endorsing any claims.





A structured analytical breakdown of the letter’s core accusations and strategic messaging. I will focus on political signaling, diplomatic framing, and implied objectives rather than endorsing any claims.

Core Accusations

1. Allegation of State Violence

The letter’s most serious charge is that the Ethiopian government is waging a systematic war against the Amhara people, allegedly marked by:

Violations of international humanitarian law

Indiscriminate killings

Aerial bombardments

Sexual violence

Attacks on civilians


Strategic meaning:
Using the language of international law elevates the conflict from a domestic insurgency to a potential international crime, implicitly inviting external scrutiny.

2. Humanitarian Catastrophe Narrative

The movement portrays the Amhara region as experiencing:

Large-scale displacement

Food insecurity

Collapse of services

Social fragmentation


Strategic meaning:
Humanitarian framing is often designed to trigger:

AU engagement

UN attention

NGO mobilization

Possible sanctions discourse


It shifts the conversation from security to human protection.

3. Delegitimization of Federal Authority

The letter argues that the current leadership has:

Failed to manage the crisis

Lost public trust

Diminished control over parts of the country


Strategic meaning:
This is classic legitimacy erosion messaging — suggesting the state is no longer fully sovereign in practice.

Such narratives are frequently used to justify:

International mediation

Transitional arrangements

Power-sharing demands

4. Implicit War-Crimes Framing

By citing “grave breaches of international law,” the letter subtly introduces the possibility of:

International investigations

Accountability mechanisms

Criminal liability


Strategic meaning:
This is not accidental — it signals an attempt to internationalize the conflict.

Once a conflict is framed in legal terms, it becomes harder for continental bodies to dismiss it as purely internal.

5. Regional Destabilization Claim

The government is accused of exporting instability through provocative foreign policy toward:

Eritrea

Somalia

The wider Horn


Strategic meaning:
This reframes Ethiopia from a victim of internal unrest to a potential regional risk, which is a far stronger trigger for AU concern.

African institutions historically react faster to threats of regional spillover than to domestic insurgencies.

Strategic Messaging Architecture

1. Self-Positioning as a Defensive Actor

The movement claims it was “compelled to defend” itself after peaceful avenues failed.

Why this matters:

This is a legitimacy-building technique aimed at portraying the group as:

reluctant fighters

politically rational

open to negotiation

Rather than ideological insurgents.

2. Appeal Over the State — Not Through It

The letter bypasses Ethiopian institutions and directly addresses the African Union.

Strategic implication:

This is a hallmark of movements seeking proto-political recognition without formally declaring themselves an alternative government.

It signals:

 “We are a political stakeholder.”

3. Institutional Language — Not Rebel Language

Notice the vocabulary:

“fact-finding mission”

“accountability mechanism”

“transitional process”

“international community”

This is the lexicon of diplomacy — not guerrilla warfare.

Strategic objective:
Rebrand the movement from militia → political actor.
4. Transitional Government Hint

The call for an “inclusive and democratic transitional process” is extremely significant.

Translation in geopolitical terms:

This implies the current government lacks legitimacy.

Movements usually escalate to this language only when seeking:

regime restructuring

negotiated power

or international mediation
5. Timing Signal
Requesting AU summit inclusion is not procedural — it is strategic.
If successful, it would:
elevate the conflict to continental agenda status
constrain Ethiopia diplomatically
create reputational pressure
What the Letter Is REALLY Trying to Achieve
Behind the humanitarian tone lies a clear strategic ladder:
Step 1 — International Attention
Step 2 — Moral Legitimacy
Step 3 — Political Recognition
Step 4 — External Pressure on Addis Ababa
Step 5 — Negotiated Power Structure
This is a familiar escalation pathway seen in multiple African conflicts.
What Is Equally Important — What the Letter Avoids

Notably absent:

No economic vision
No governance roadmap
No territorial clarity
No foreign policy outline
This suggests the message is primarily reactive and diplomatic, not programmatic.
Movements that aspire to govern typically begin articulating state-like capacities.
Strategic Assessment (Neutral)
From an intelligence-analysis perspective, the letter is less about immediate intervention and more about narrative positioning.
It attempts to move the conflict from:
 Internal rebellion → continental concern.
Whether it succeeds depends on three factors:
1. Credibility of the allegations
2. Regional stability risks
3. Ethiopia’s diplomatic counterweight

Monday, December 29, 2025

When Algorithms Rival Flags: Why the 21st Century’s Real Power Struggle Is No Longer Between States



When Algorithms Rival Flags: Why the 21st Century’s Real Power Struggle Is No Longer Between States

By any historical measure, it is extraordinary that the head of Britain’s foreign intelligence service would warn not primarily about rival nations, but about technology companies.

     Blaise Metreweli

Yet that is precisely what Blaise Metreweli, in her first public speech as chief of MI6, has done. Her message was unambiguous: power in the modern world is shifting, and some of it no longer flies under a national flag.

“Our world is being remade,” Metreweli said, by technologies that once belonged to the realm of science fiction. Algorithms, she warned, can now “become as powerful as states.”

This is not a rhetorical flourish. It is a sober intelligence assessment.

From Westphalia to Silicon Valley

For over three centuries, the international order has been built on a simple assumption: sovereign states monopolise power. Armies, borders, diplomacy, and law all flowed from that premise. Even multinational corporations, however wealthy, ultimately operated under state authority.

That assumption is now eroding.

Today’s technology giants command resources larger than the GDPs of many nations. They shape information flows for billions of people, influence elections without casting a single vote, and can destabilise societies faster than any traditional weapon. Their leaders are unelected, largely unaccountable, and often transnational—answering to shareholders rather than citizens.

When an algorithm determines what people see, believe, fear, or ignore, it does not merely mediate reality; it also shapes their perceptions of it. It constructs it.

Algorithms as Instruments of Power

Metreweli’s most striking warning was not about hardware or weapons, but about software. Social media algorithms, she noted, can rival states in power. This is not hyperbole.

Algorithms determine which conflicts persist and which fade away. They can amplify outrage, radicalisation, and misinformation at machine speed. In times of crisis, they can inflame ethnic tension, undermine public trust, and paralyse governments—without firing a shot.

In effect, algorithmic systems have become instruments of geopolitical influence, capable of reshaping societies from the inside. Unlike conventional power, they operate invisibly, continuously, and globally.

And unlike states, they are rarely constrained by democratic oversight.

The New Theatre of Conflict

Metreweli is right to argue that technology is “rewriting the reality of conflict.” War is no longer confined to battlefields. It unfolds in data centres, recommendation engines, and digital platforms.

Cyber operations, deepfakes, automated surveillance, and AI-driven targeting blur the line between war and peace. The result is a permanent grey zone—where manipulation replaces invasion and perception replaces territory.

In this environment, the most decisive battles are fought not over land, but over attention, narrative, and truth.

The Question That Matters Most

Perhaps the most crucial line in Metreweli’s speech was this: the defining challenge of the 21st century is not who wields the most powerful technologies, but who guides them with the most incredible wisdom.

This reframes the debate entirely.

The problem is not technology itself. It is governance. Power without wisdom has always been dangerous—whether held by emperors, generals, or corporations. What is new is the speed, scale, and opacity with which technological power now operates.

We have allowed private entities to accumulate state-like influence without state-like responsibility. That imbalance is no longer sustainable.

A Call for Democratic Reassertion

Metreweli’s warning should be read as a call to action—not just for intelligence agencies, but for democratic societies.

Governments must reclaim their regulatory role. Citizens must demand transparency and accountability. International norms must evolve to address algorithmic power, just as they have in the past to address nuclear weapons and financial systems.

The alternative is a world where unelected executives and inscrutable code shape global outcomes more decisively than parliaments or voters.

That would not be progress. It would be a quiet abdication of democracy.

Ultimately, flags still hold significance. But in the age of algorithms, wisdom—ethical, legal, and political—matters more than ever. The question is whether democracies will rise to that challenge, or sleepwalk into a future governed not by laws, but by lines of code.


Blaise Metreweli is a senior British intelligence officer who made history in 2025 by becoming the first woman to serve as Chief of the Secret Intelligence Service (MI6).

Who is Blaise Metreweli?

Blaise Metreweli is a career intelligence professional with decades of experience across the UK’s security architecture. Before assuming leadership of MI6, she held senior roles within Britain’s intelligence and national security ecosystem, including positions focused on counter-terrorism, cyber threats, and strategic intelligence assessment.

Her appointment itself reflects a broader shift within Western intelligence agencies: from Cold War–era state-to-state espionage toward complex, multi-actor threats involving technology firms, non-state networks, and digital platforms.

Why Her Words Matter

As MI6 chief, Metreweli speaks not as a commentator but as the custodian of Britain’s external intelligence priorities. When she warns that:

Big tech firms rival nation-states in power, and

Algorithms can shape conflict, perception, and sovereignty,

She is signalling an institutional recalibration within Western intelligence thinking.

This is not speculative philosophy; it is threat assessment

Strategic Significance of Her First Speech

Metreweli’s emphasis on:

algorithmic power,

AI-driven influence,

and the ethical governance of technology

Marks a departure from traditional intelligence rhetoric, which has focused on rival governments alone.

It acknowledges that power in the 21st century is increasingly privatised, digitised, and borderless—often escaping the constraints of international law, diplomacy, or democratic accountability.

 Blaise Metreweli, the first woman to lead MI6, has issued a stark warning of a new global order in which algorithms and tech executives rival states in power—raising urgent questions not of capability, but of wisdom and control.